External News and ActivitiesFebruary 9, 2024 216 Subheaderየፕሮጀክቱ እንቅስቃሴ አበረታች እንደሆነ ተገለፀⵑⵑ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ስራ አስፈጻሚ ትኩረቱን በሴቶች ላይ ያደረገው Women, Coffee and Climate ፕሮጀክት አጠቃላይ ሲያከናውናቸው በቆዩ ተግባራት ዙሪያ ክብርት የኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ∕ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው፣ ክቡር ዋና ዳይሬክተር ዶ∕ር አዱኛ ደበላ፣ የስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን ሀላፊ እንዲሁም በስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን የአፍሪካና ኢስያ ፕሬዝደንት በተገኙበት ሰፊ ገለጻ ተደርጓል∶∶ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚገኘው የቡና ማሰልጠኛ ማእከልም ተጎብኝቷል∶∶ፕሮጀክቱ በስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን ድጋፍ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ደን ልማት፣ የምስራቅ አፍሪካ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት እንዲሁም ውመን ኢን ኮፊ በቅንጅት የሚያከናውኑት እንደሆነ አቶ ፍጹም መንገሻ በባለስልጣን መ∕ቤቱ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ስራ አስፈጻሚ ተናግረዋል∶∶ በኢሉባቦር ዞን ቡና አምራች በሆኑ 5 ወረዳዎች ትኩረቱን ያደረገው ይህ ፕሮጀክት ሴቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ሊደርስባቸው የሚችለውን ጉዳት ከመቀነስ አንጻር በግብአት አቅርቦት፣ በስልጠናና አቅም ግንባታ፣ ማህበረሰብ አቀፍ ውይይት፣ የእውቀት ሽግግር፣ እንዲሁም ሴቶችን በማብቃት በኩል የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱ ተብራርቷል∶∶ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በተደረጉ የተለያዩ ጥናቶች የታዩ ግኝቶችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል∶∶ይህ በስፓኒሽ ኮኦፐሬሽን በአገራችን ተግባራዊ በመደረግ ላይ የሚገኝ ፕሮጀክት በሌሎች አገራት ከሚከናወኑ መሰል በርካታ ፕሮጀክቶች አንጻር 12ኝነት ደረጃ ማግኘቱ አበረታች እንደሆነም በውይይቱ ተነስቷል∶∶ Share